የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሠራተኞች ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ለገሱ - National Bank

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሠራተኞች ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ለገሱ

አዲስአበባ፣ ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሠራተኞች ለአገር መከላከያ ሠራዊት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታወቁ።
የባንኩ ማኔጅመንት አባላትና መላ ሠራተኞች ዛሬ ባካሄዱት ስብሰባ ለጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን የሚሆን ከደጀንነት እስከ ግንባር መሰለፍ የሚደርስ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
ሠራተኞቹ የአንድ ወር ደመወዛቸውን ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ሠጥተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ቀደም ሲል ሲያደርጉት እንደቆዩት ሁሉ ደም መለገሳቸውን እንደሚቀጥሉበት አረጋግጠዋል።
ሠራተኞቹ ከደጀንነት በተጨማሪ ግንባር ድረስ በመሄድ ከሠራዊቱ ጎን በመሰለፍ የሕይወት መስዋዕትነት ለመክፈል መዘጋጀታቸውንም አስታውቀዋል።  ወደ ግንባር ለመዝመት ተመዝግበው ለመሄድ የተዘጋጁ የባንኩ ባልደረቦች መኖራቸውም ታውቋል።
ሠራተኞቹ ለሠራዊቱ በቀጥታ ከሚያደርጉት ድጋፍ ጎን ለጎን በተሠማሩበት የሙያ መስካቸው የበለጠ በመትጋት ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።

The National Bank of Ethiopia was established in 1963 by proclamation 206 of 1963 and began operation in January 1964.

P.O.Box: 5550
Tel: +251 115 517 430
E-mail: nbeinfo@nbe.gov.et
Fax: +251 115 514 588
Avenue: Sudan Street

Navigation

Follow Us