Mamo Esmelealem Mihretu, Biography

Mamo E. Mihretu is the 10th Governor of the National Bank of Ethiopia (NBE). Before he was appointed as the Governor of NBE, Mr. Mamo served as the founding CEO of the Ethiopian Investment Holdings (EIH), the strategic investment arm of the government of Ethiopia. EIH manages all key commercial companies of the government of Ethiopia, such as Ethiopian Airlines and EthioTelecom.

Mr. Mamo is a member of Ethiopia’s Macroeconomic Council, which is the body that steers economic policy and strategic decisions. He has been a member and a Secretary of the Council for the last four and half years. He was an active member of the economic team that conceptualized, developed and implemented Ethiopia’s economic reform program.

As a Board member of the Commercial Bank of Ethiopia (CBE) for four years, the largest financial institution in the country, Mr. Mamo chaired CBE’s transformation program.

Mr. Mamo also served as a Senior Policy Advisor to the Prime Minister of Ethiopia and Ethiopia’s Chief Trade Negotiator from 2018-2021.While working at the Office of the Prime Minister, Mr. Mamo helped  create the policy and performance department that oversees performance outcomes of government agencies. Before joining the Ethiopian government in 2018. Mr. Mamo was a Senior Project Manager at the World Bank Group in Kenya from 2010 to 2018, working mainly on finance and competitiveness issues. Mr. Mamo obtained a Master’s Degree in Leadership, Public Administration and Economic Development from the Kennedy School of Government of Harvard University in the United States. He also holds a post-graduate degree in Trade and Investment from the Universities of Pretoria and University of Amsterdam. He was a gold medalist when he graduated from Addis Ababa University, School of Law.

 

የባንኩ ሴት ሠራተኞች ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ

የባንኩ ሴት ሠራተኞች ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሴት ሠራተኞች የዘንድሮውን የዓለም የሴቶች ቀን በድምቀት አከበሩ። ቀኑ “እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ቃል በአገርአቀፍ ደረጃ ለ47ኛ ጊዜ ተከብሮ ውሏል።

የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በባንኩ አዳራሽ የተከናወነውን ሥነሥርዓት በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የኮርፖሬት ሰርቪስ ም/ገዥ አቶ እዮብ ገብረኢየሱስ ዕለቱ ተከብሮ የሚውለው ለሴቶች የማይመቹ ሁኔታዎችን ማስወገድና በተለያየ መልክ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን መታገል እንደሚገባ ለማስገንዘብ መሆኑን ገልጸዋል።

በርግጥም “እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚለው መሪ መልዕክት መሠረት ሁላችንም ጭቆናና ጥቃቶችን ልንታገላቸው ይገባል ብለዋል።

በተቋም ደረጃ ለሴቶች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር፣ አቅማቸውን ማሳደግና ወደ ሥልጣን ማምጣት የባንኩ አመራር የሚረዳው ጉዳይ ነው ያሉት ም/ገዢው፣ ሴቶችም በበኩላቸው ለዚህ አስተዋፅኦ ማድረግና ዝግጁ ሆኖ መገኘት እንደሚኖርባቸው አመልክተዋል።

የባንኩ የሴቶችና ወጣቶች ጉዳይ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት ወይዘሮ አምባወርቅ መኮንን ዕለቱን አስመልክቶ በሠጡት ገለጻ የሴቶችን ጉዳይ በሁለንተናዊ መልኩ ለመድረስ የማያቋርጥ ትግል እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል።

ዕለቱ በአገራችን ለ47ኛ፣ በዓለምአቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ112ኛ ጊዜ ቢከበርም፣ አሁንም በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት አልቀረም፤ ሴቶችን ማጎናጸፍ የሚገባው ድል ገና በሚገባ ማሳካት አልተቻለም ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዕለቱን አስመልክቶ ቀደም ካሉት ዓመታት ጀምሮ ያደካሄዳቸውን መርሐግብሮች ያስታወሱት ወይዘሮ አምባወርቅ፣ በተጓዳኝም የባንኩን ሴት ሠራተኞች ከቁጥር፣ ከትምህርት ዝግጅትና አመራር ላይ ካላቸው ተሳትፎ አኳያ በአሀዝ በተደገፈ መረጃ ማብራሪያ ሠጥተዋል።

በመርሐግብሩ መሠረት ከባንኮች ክሊኒክ የመጡ ዶክተሮች በማህጸን ጫፍ ካንሰርና በጡት ካንሰር ላይ ትምህርታዊ ገለጻ የሠጡ ሲሆን፣ ከኦፕሪፍስ መጠለያ ማዕከል በመጡ ሕጻናት ኪናዊ ዝግጅት ቀርቧል፤ የዳቦ ቆረሳና ቡና የማፍላት ሥነሥርዓትም ተካሂዷል።

የኦፕሪፍስ ማዕከል ሀላፊ ወይዘሮ እንግዳወርቅ ታደሰ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀደም ሲል በህዳር 2015 ዓ.ም በማዕከሉ ተገኝቶ ያደረገውን ጉብኝትና ድጋፍ አስታውሰው፣ በቀጣይም ባንኩ ለማዕከሉ የሚያደርገው ድጋፍ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ሁሉም ወላጅ ልጆቹን (ሴቶችንም ሆነ ወንድ ልጆቹን) በቤትም ሆነ በውጭ፣ እንዲሁም ከቅርብ ዘመድም ጭምር መጠበቅ እንዳለበት ማዕከሉ የሚንከባከባቸው የጥቃት ሰለባ ሕጻናት መልክዕት መሆኑን ወይዘሮ እንግዳወርቅ አሳስበዋል። ምክንያቱም አብዛኞቹ ጥቃቶች ከሩቅ ሳይሆን ከቅርብ በተለይም “የእኔ” ከሚሉት ወገን የሚመጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የለውጥ ማኔጅመንት፣ ዕቅድና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አባተ ምትኩ እንዳሉት፣ “እኔም የእህቴ ጠባቂ ነኝ” የሚለውን መሪ ቃል ሁሉም ከልቡ ተግባራዊ ማድረግ አለበት።

በተቋም ደረጃ ሴት ሠራተኞችን በአቅም ግንባታ ከማሳደግና ወደ አመራር ሠጪነት እንዲበቁ ከማድረግ ጎን ለጎን ባንኩን ለሴቶች አመቺ የሥራ ቦታ እንዲሆንላቸው ሁሉንም አስቻይ ነገሮች ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

የሕጻናት ማቆያ (day care) ማዕከሉን ግንባታና ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቅቆ በፍጥነት ሥራ ላይ ማዋል የሚያስፈልግ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አባተ፣ ይህም የባንኩ ሴት ሠራተኞች ሥራቸውን በተረጋጋና በውጤታማነት እንዲያከናውኑ ለማስቻል በእጅጉ የሚያግዝ መሆኑን አብራርተዋል።

በተጨማሪም ነፍሰጡር እናቶች በመንግሥት የተሠጣቸው የወሊድ ፈቃድ አጠቃቀም ላይ በራሳቸው በነፍሰጡሮቹ ፍላጎት መሠረት ተመቻችቶ ተግባራዊ ቢደረግ መልካም መሆኑን አቶ አባተ ጠቁመዋል።

በዓመት አንድ ጊዜ በሚከበረው በሴት የሴቶች ቀን ላይ የባንኩ መካከለኛና ከፍተኛ ሴት አመራር አባላት እንደሚጠበቀው አለመሳተፋቸውን እንደክፍተት አንስተውታል።           አቶ አባተ በየዓመቱ መጠነኛም ቢሆን ለተለያዩ ግብረሰናይ ድርጅቶች ድጋፍ እየሠጠንና ደማቅ በሆነ ሁኔታ እንድናከብር ለሚፈቅድልን የባንኩን የበላይ አመራር፣ እንዲሁም ጥሪያችንን አክብረው በበዓሉ ላይ ለሚታደሙ ሠራተኞች፣ በማህጸን ጫፍ ካንሰርና በጡት ካንሰር ላይ ትምህርታዊ ገለጻ ለሰጡት ዶክተሮች በመጨረሻም ለኦፕሪፍስ ማዕከል ምሥጋና አቅርበዋል።

የባንኩ ሠራተኞች 127ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከበሩ

የባንኩ ሠራተኞች 127ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከበሩ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት 127ኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት አከበሩ።

የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በባንኩ አዳራሽ በተከናወነው ሥነሥርዓት ላይ የማኔጅመንት አባላትና የባንኩ ሠራተኞች፣ የተገኙ ሲሆን፣ በልዩ ልዩ ሁነቶች መርሐግብሩ ተከናውኗል።

መርሐግብሩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የኮርፖሬት ሰርቪስ ም/ገዥ አቶ እዮብ ገብረኢየሱስ የአድዋ ድል ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያን ብሎም ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት ተምሳሌት መሆኑን ገልጸዋል።

የአድዋ ድል ጥቁር ሕዝብም አሸናፊ እንደሆነ ለነጮቹም ሆነ ለመላው ዓለም ትምህርት የሠጠ መሆኑንና ለጸረ-ኮሎኒያሊዝም ትግል መነሻ ሊሆን እንደቻለ ታላላቅ ምሁራንና የአገራት መሪዎች ያረጋገጡት ጉዳይ መሆኑንንም አቶ እዮብ  አብነት ጠቅሰው አስረድተዋል።

ም/ገዢው እንዳስረዱት ከኔልሰን ማንዴላ ቀጥሎ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉት ታቦ ምቤኪ በአንድ ወቅት ባደረጉት ገለጻ የአድዋ ድል ለነጮች የሚያስደነግጥ ትምህርት የሠጠ፤ ለተቀረው የዓለም ሕዝብ የነፃነት ፋና ወጊ መሆን የቻለ ትልቅ የታሪክ ክስተት መሆኑን አስረድተዋል።

“በመሆኑም የዘንድሮውን 127ኛ የአድዋ ድል በዓል ስናከብር አባቶቻችን ምን ያህል አኩሪ ታሪክ ሠርተው ያለፉ መሆኑን የምናስታውስበትና እኛም በአንድነት፣ በጀግንነትና በጽናት ታሪክ መሥራት የሚጠበቅብን መሆኑን ያስረዳል” ሲሉ አቶ እዮብ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የለውጥ ማኔጅመንት፣ ዕቅድና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አባተ ምትኩ አድዋን በተመለከተ ባቀረቡት አጭር ገለጻ፣ አድዋ በአባቶቻችን ከፍተኛ ተጋድልዎ የተደረገበትና በሚያስደንቅ ጀግንነት ድል የተገኘበት ጦርነት መሆኑን አስረድተዋል።

አቶ አባተ በገለጻቸው ስለ ጠርነቱ መንስዔ፣ ስለጣሊያኖች ዝግጅት፣ በአፄ ምኒልክ ስለተደረገው ጥሪ፣  እቴጌ ጣይቱ ለጣሊያን መንግሥት ስላስተላለፉት መልዕክት፣ ስለሃይል አሰላለፍ በመጨረሻም ስለተካሄደው ጦርነትና አባቶቻችን ስለተጎናጸፉት ድል አብራርተዋል።

በመርሐግብሩ በኢትዮጵያ ሴት ደራሲያን ማህበር አማካኝነት ኪናዊ ዝግጅት የቀረበ ሲሆን፣ የዳቦ ቆረሳ፣ ቡና የማፍላት ሥነሥርዓት መካሄዱ ለዝግጅቱ ድምቀት ሆኗል።

በመርሐግብሩ ማጠናቀቂያ ላይ አድዋን በተመለከተ የጥያቄና መልስ ውድድር የተካሄደ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ም/ገዥና ዋና ኢኮኖሚስት ለተወዳዳሪዎች የተዘጋጀውን ሥጦታ ሸልመዋል።

ም/ገዢው አቶ ፍቃዱ ድጋፌ በመጨረሻ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያውያን በየትኛውም ጊዜ በአገር ላይ የሚመጡ የውጭ ጥቃቶችን ለመቀልበስ በአንድነት የሚነሱ መሆናቸውን የአድዋ ድል ትክክለኛ ማሳያ መሆኑን አመልክተዋል። በመሆኑም በአድዋ ጦርነት ወቅት በአባቶቻችን ዘንድ የታየውን አንድነት፣ ጀግንነትና ጽናት አሁን ደግሞ እኛ ድህነትን ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት ላይ መረባረብ እንዳለብን ምክትል ገዥው አሳስበዋል።

“የተረጋጋ የውጭ ምንዛሬና ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት እንዲኖር ይሠራል”

የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ ገዥ
ኤልያስ ሳላህ

የተረጋጋ ዋጋና የውጭ ምንዛሬ እንዲሁም ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት የማክሮኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት በመሆናቸው የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ እነርሱ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አዲሱ የባንኩ ገዥ አቶ ማሞ እስመለዓለም ምህረቱ ገለጹ፡፡ ከፋይናንስ ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች ጋርም በዘርፍ የ 6 ወር አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ጥር 24 ቀን 2015 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲሱ ህንፃ ዋናው አዳራሽ በተካሄደው ውይይት ላይ አቶ ማሞ የፋይናንስ ዘርፉ ብቻውን የቆመ ሳይሆን ከማክሮኢኮኖሚ ጋር ተያይዞ የሚጓዝ መሆን እንዳለበት አመልክተዋል፡፡ በዚህ ዓመት በ 7 ነጥብ 5 በመቶ ያድጋል ተብሎ ለሚጠበቀው የአገሪቱ ኢኮኖሚ የፋይናንስ ሴክተሩ የራሱ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል፡፡ የባንኩ ዋነኛ ተልዕኮዎች የሆኑትን ዋጋ የማረጋጋትና የውጭ ምንዛሬ ተመን የማስፈን እንዲሁም ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት የመፍጠር ጥረት በቀጣይ የባንኩ ዋነኛ ትኩረቶች እንደሚሆኑ የጠቆሙት አቶ ማሞ፣ በቀጣይም የዋጋ ንረትን እንዳያባብስ በገንዘብ ፖሊሲው አማካኝነት የተጠና ሥራ እንደሚሠራም አስታውቀዋል፡፡ የፋይናንስ ዘርፉ በአጠቃላይ፣ በተለይም የባንክ ዘርፉ በአገር ዕድገት ላይ እያደረገ ያለውን አስተዋጽኦ ያነሱት ዋና ገዥው፣ ለአብነትም ባለፉት ስድስት ወራት ከ157 ቢሊዮን ብር በላይ የግምጃ ቤት ሰነድ መግዛቱን አመልክተዋል። ይህም የበጀት ጉድለትን በመሙላት ረገድ የፋይናንስ ዘርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ ያለው አስተዋጽኦ እየጨመረ መሆኑን እንደሚያሳይ የጠቆሙት አቶ ማሞ፤ ባንኮች የሚሰበስቡት የተቀማጭ ገንዘብ፣ ሃብትና የሚሰጡት ብድር በየዓመቱ በአማካይ በ30 በመቶ እያደገ ስለመሆኑም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ከባንክ ውጭ ያለው ገንዘብ ከ189 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ጠቁመው ይህም ለባንኮች ተጨማሪ ሃብት ለማሰባሰብ እድል የሚፈጥር እንደሆነ አመልክተዋል፡፡

የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የቦርድ አባላት ሥራ ጀመሩ

    • ይናገር ደሴ (/) የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሹመዋል

 

በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ አህመድ የተሾሙት የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የቦርድ አመራር አባላት ሥራ ጀመሩ።

በቅርቡ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይጠበቅ የነበረውን የካፒታል ገበያ ባለሥልጣንን የሚያገለግሉ ስድስት የቦርድ አባላት ኅዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም. መሾማቸው ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ይናገር ደሴ (ዶ/ር) የቦርዱ ሰብሳቢ ሆነው ተሹመዋል።

ሌሎቹ የቦርዱ አባላት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድምአገኝ ነገራ፣ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ፣ ከተመድ የካፒታል ዴቨሎፕመንት ኢትዮጵያ ጽሕፈት ቤት ደግሞ (ዶ/ር)ኢዮብ ተስፋዬ ፣የሒሳብና የኦዲት ቦርድ ዋና ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሒክመት አብደላ፣ የሴሬብሩስ ፍሮንቲየርስ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ ኃይለ ሚካኤል እና የአዲስ አበባ ዩነቪርሲቲ መምህር አቶ አባተ አበበ ናቸው፡፡

ከኅዳር 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ የባለሥልጣኑ የቦርድ አባል ሆነው እንዲሠሩ የተመደቡት እነዚህ የቦርድ አባላት ማክሰኞ ኅዳር 27 ቀን 2015 የመጀመሪያ ስብሰባቸውን አካሂደው ሥራቸውን ጀምረዋል።

እነዚህ ተሿሚዎች በቦርድ አባልነት የተሰየሙት በካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1248 /2013 መሠረት ሲሆን፣ በአዋጁ መሠረት የቦርድ አባላቱ የሥራ ዘመን አምስት ዓመት እንደሆነ ተደንግጓል፡፡

በአዋጁ መሠረት የካፒታል ገበያ ማቋቋም ያስፈለገው ካፒታል በማሰባሰብ፣ የገንዘብ ሥርዓቱን በአዲዲስ ፈጠራዎች በመደገፍ እና የኢንቨስትመንት ስጋቶችን የመጋራት አሠራርን በማስፋፋት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ልማት ለመደገፍ እንዲቻል ነው። በተጨማሪም በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ላይ  የሚፈጠሩ መዋቅራዊ ስጋቶችን ለመለየት፣ ለመከላከልና  ለመቀነስ በካፒታል ገበያ ላይ ጠንካራ የቅርብ ክትትልና የቅኝት ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት በማስፈለጉ መሆኑን በአዋጁ ተደንግጓል።

 

የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ሥራ ሊጀምር ነው

የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ሥራ ሊጀምር ነው

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድን (Deposit Insurance) ሥራ ለማስጀመር የሚስችሉ የዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ የሚኒስተሮች ምክር ቤት ባጸደቀው ደንብ ቁጥር 482/2013 መሠረት መቋቋሙን ተከትሎ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ፈንዱን በበላይነት የሚመሩ አምስት የቦርድ አባላትን ሾመዋል።

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ተቋማት ሱፐርቪዥን ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ በሰብሳቢነት የተሾሙ ሲሆን፣ የባንክ ሱፐርቪዥን ዳይሬክተር አቶ ፍሬዘር አያሌው፣ አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት ሱፐርቪዥን ዳይሬክተር አቶ መርጋ ዋቅወያ፣ የዘመን ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ደረጃ ዘበነ፣ እንዲሁም የአነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሾመ ከበደ የቦርዱ አባል ሆነው እንዲሰሩ የተመደቡ መሆናቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተላከው ደብዳቤ አመልክቷል።

የቦርዱ አባል አቶ ፍሬዘር አያሌው ለዜና ኢብባ እንደገለጹት፣ ፈንዱን ሥራ ለማስጀመር እንዲቻል ፖሊሲ ፕሮሲጀርና መዋቅር የማዘጋጀት፣ ሃላፊ የመመደብና ሠራተኞች የማሟላት እንዲሁም የፈንድ ካፒታል የማሰባሰብና ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈንዱ ራሱን ችሎ እስኪደራጅ ድረስ የቢሮ ዕቃዎችን የማሟላትና ሠራተኛ የመቅጠር ሃላፊነቱን እንደሚወጣ አቶ ፍሬዘር ጠቁመዋል።

የፈንዱ አባላት ከሕብረተሰቡ ተቀማጭ ገንዘብ የሚሰበስቡ የፋይናንስ ተቋማት (ባንኮችና አነስተኛ የገንዘብ ተቋማት) መሆናቸውን አቶ ፍሬዘር አመልክተዋል።

የፈንዱ ገንዘብ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሚከፈት ሂሳብ ውስጥ የሚቀመጥ ሲሆን፣ ሁሉም አባል የፋይናንስ ተቋማት በፈንዱ የሚወሰነውን መነሻ የዓረቦን ክፍያ ወደ ፈንዱ ሂሳብ ገቢ ያደርጋሉ። መንግሥትም መነሻ ካፒታል እንዲሆን ለፈንዱ ሁለት መቶ ሚሊዮን ብር እንደሚመድብ ደንቡ ደንግጓል።

ፈንዱ የተለያዩ የሀብት መሰብሰቢያ መንገዶችን መጠቀም እንደሚችል በደንቡ ውስጥ የተደነገገ ሲሆን፣  የዓረቦን ክፍያዎችን ከአባል የፋይናንስ ተቋማት እንዲሁም የተለያዩ መዋጮዎችን እንደመንግሥትና የልማት አጋሮች ካሉ ሌሎች ምንጮች መሰብሰብና ወደ ራሱ ገቢ ማድረግ እንደሚችል ሥልጣን ተሠጥቶታል።

ፈንዱ ከወደቁ ወይም ከፈረሱ የፋይናንስ ተቋማት ንብረት ማጣራት ከሚገኝ ተመላሽ ገንዘብና በቦርዱ ከሚፀድቁ ሌሎች የፋይናንስ ምንጮች ከሚገኝ ገንዘብ ተጠቃሚ ይሆናል። የፈንዱን ሀብት ገቢ በሚያስገኙለት ዘርፎች ኢንቨስት የማድረግና የማስተዳደር መብት እንዳለውም ተደንግጓል።    

ፈንዱን ማቋቋም ያስፈለገው በኢትዮጵያ ቀጣይ የኢኮኖሚ እዴገት የሀገሪቱን የፋይናንስ ሥርዓት ጤናማ፣ ለአደጋ ያልተጋለጠና የተረጋጋ በማድረግ ለማጠናከርና የገንዘብ አስቀማጮች ጥበቃ ለፋይናንስ ሥርዓት ለማረጋጋት በተጨማሪም የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድን እንደ አንድ ተጨማሪ የሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ማረጋጊያ ለማድረግ መሆኑ በደንቡ ተመልክቷል። የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ራሱን የቻለ ሕጋዊ ሰውነት ያለው ተቋም ሲሆን፣ ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መሆኑን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያወጣው ደንብ ደንግጓል።

NBE Issues a Directive that limits Birr and Foreign Currency Holding

NBE Issues a Directive that limits Birr and Foreign Currency Holding

Addis Ababa/ 06/05/2022. National Bank of Ethiopia (NBE) has issued a Directive to limit on Birr and Foreign Currency Holding in the territory of Ethiopia.
Signed by H.E. Dr. Yinager Dessie, the Governor of the National Bank of Ethiopia (NBE), the Directive FXD/81/2022, shall enter into force as of September 05, 2022.
The Directive states that it has become necessary to limit the Birr holding amount for a person entering into and departing from Ethiopia. Besides, it’s necessary to set conditions, limitations, and circumstances under which an Ethiopian, resident of Ethiopia, and a non-resident or any other person who may process and utilize foreign currency.
According to the Directive a person entering into and departing from Ethiopia may hold up to maximum of Birr 3,000.00 (Birr Three Thousand) per travel to and from Ethiopia. However, a person travelling to Djibouti may hold up to a maximum amount of Birr 10,000 (Birr Ten Thousand) per travel.
A person residing in Ethiopia enters to the territory of Ethiopia shall convert all foreign currency he/she is carrying at an authorized forex bureau for the equivalent sum in Birr, or deposit to his/her foreign currency account within 30 days of entry to the territory.
However, he/she has to present custom declaration if the foreign currency amount exceeds USD 4,000 (USD Four Thousand) or equivalent in any other convertible foreign currency while depositing into foreign currency account.
The Directive put also the time limit for holding and conversion of foreign currency for the Foreign national of Ethiopian Origin or Ethiopian National not residing in Ethiopia who enters the territory carrying foreign currency. If he/she carries foreign currency and intends to stay more than ninety days, shall deposit the money into his/her Non-resident (NR) foreign currency account.
However, if the amount of the foreign currency exceeds USD 10,000 (USD Ten Thousand) or equivalent in any other convertible foreign currency, he/she has to present custom declaration to deposit or convert it to Birr at an authorized forex bureau.
In addition, the Directive states that a person residing in Ethiopia is allowed to travel abroad by carrying a foreign currency if he/she present a bank advice issued for the purchase of the foreign currency within thirty (30) days from the bank advice.
When non-resident foreign national of Ethiopian origin and Ethiopian National not residing in Ethiopia enters into the territory of Ethiopia carrying a foreign currency from abroad and travel back within 90 days from the date of entry stamped on the travel document by the Immigration and Citizenship Service, he/she has to present custom declaration, if the foreign currency amount exceeds USD 10.000 (USD Ten Thousand) or equivalent in any other convertible foreign currency.
A person entering into the territory of Ethiopia from a neighboring country using land transport carrying other foreign currency having a value of more than or equivalent of USD 500 (USD Five Hundred), shall declare at the boarder custom branches, and may travel by carrying such declared amount.

For detail information, you can see from the Directive FXD/81/2022 uploaded in this website.

Banks in Ethiopia Continue to Grow Despite Challenges

Addis Ababa August09/2022/:- The Ethiopian banking sector has registered a remarkable growth despite the fact that it faced various challenges such as COVID-19, internal conflict, and the Ukraine-Russia crisis, Dr. Yinager Dessie said.
In a meeting held with CEOs of banks, on 8th August 2022 at Hilton Hotel, H.E. Dr. Yinager Dessie, Governor of the National Bank of Ethiopia (NBE), said that the banking sector has continued to registering growth in asset, capital, deposit, loan distribution, loan collection and other financial growth indicators.
“In terms of financial soundness,” the Governor added “ as indicated in Capital Adequacy Ratio, Liquidity and Non-Performing Loan (NPLs), the banking sector is healthy sound.
The Governor said “Over the last four years, NBE did embark on various policy issues, which help to address bottleneck and lingering problems in the financial sector” Proclamations, directives, and other legal instruments were issued, and amended. Besides, exchange rate, interest rate and demonetization were also among the major endeavors.”
With regard to the banking sector, and digital financial system, Ato Frezer Ayalew, Director of Banking Supervision, and Ato Solomon Damtew, Director of Payment Settlement and System, explained that remarkable progress have been registered.
According to Ato Ferezer, the number of banks has increased from18 to 30, and their branches reached to 8,944, as of June 30, 2022, from 5,564 four years ago.
With the expansion of bank branches, the ratio of branch per population reached to 1: 11, 516 (one bank branch serves 11, 516 people). Besides, the number of deposit accounts has increased from 40.04 billion birr to 83.3 billion birr. Hence, the total deposits, over the last four years, have increased from 899 billion in 2019, to 1.7 trillion Birr in 2022.
The total capital of the banks has boosted from 98.9 billion in 2019 to 199.1 billion birr in 2022. The growth registers 27 percent average yearly growth. Moreover, total asset of banks has ascended from 1.3 trillion birr to 2.4 trillion Birr registering 92 percent growth.
Net income of banks has increased from 22.4 billion birr in 2019 to 49.9 billion birr in 2022 registering 122 percent growth, as it was indicated.
According to NBE, the banks have continued to operate in a safe and sound manner, though there is a need for strengthening advanced preparation for opening banking sector to foreign investors was emphasized.
Appreciating the progress registered over the past four years, presidents and CEO’s of the banks suggested to join hands to building human capital and to mitigating illegal acts in financial sector.
Currently 29 commercial banks, one development bank, 18 insurance companies, one re-insurance company, 40 microfinance institutions, six Capital goods Finance/Lease companies, and eight payment instrument issuers/system operators are operating in Ethiopia.

The National Bank of Ethiopia was established in 1963 by proclamation 206 of 1963 and began operation in January 1964.

P.O.Box: 5550
Tel: +251 115 517 430
E-mail: nbeinfo@nbe.gov.et
Fax: +251 115 514 588
Avenue: Sudan Street

Navigation

Follow Us