የኢትዮጵያ መንግሥት አዳዲስ የደህንነት ገጽታዎች እና ሌሎችም መለያዎች የተካተቱባቸው የገንዘብ ዓይነቶችን ለግብይት እንደሚያውል በዛሬው ዕለት ተገልጿል። ነባሮቹ የ10፣ የ50 እና የ100 ብር የገንዘብ ዓይነቶች ሙሉ ለሙሉ የሚተኩ ይሆናል። አዲስ የ200 ብር ገንዘብም በተጨማሪነት ለግልጋሎት ይውላል። የ5 ብር ገንዘብ ባለበት ቀጥሎ፣ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ወደ ሣንቲም የሚለወጥ ይሆናል። ይህ የገንዘብ ቅያሪ መደበኛ ባልሆነ መንገድ እንዲሁም ከፋይናንስ ተቋማት ውጪ የሚዘዋወረውን ገንዘብ ለመሰብሰብ፣ ሙስናን እና የኮንትሮባንድ ሥራዎችን ለመቀልበስ የታለመ ነው። የፋይናንስ ተቋማት የገንዘብ እጥረትን ለመቋቋም እንዲችሉም ያግዛል።
በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የሕትመት ሥራ ተገባዶ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ግምጃ ቤት ይገኛል። የስርጭት ስርዓት እና ዕቅድ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በሚመለከታቸው አካላት አማካኝነት የሚተገበር ይሆናል። በገንዘብ ቅያሬው ሂደት የጸጥታ ማስከበር አካላት ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ከማኅበረሰቡ ጋር በመተባበር ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ያስፈጽማሉ። ከብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት፣ ከብሔራዊ የመረጃ እና ደህንነት አገልግሎት እና ከፌደራል ፖሊስ የተውጣጣ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሞ፣ ሂደቱን በበላይነት ያስተባብራል። የክልል መንግሥታትም ተመሳሳይ ኮማንድ ፖስት አቋቁመው ሥራውን እንዲያከናውኑም ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ ገንዘቧን የሚወክል ምልክት እንዳልነበራት ይታወቃል። በቅርቡ ለብር መለያ የሚሆን አዲስ ምልክት ተዘጋጅቶ በጥቅም ላይ ይውላል።
The government of Ethiopia has introduced new currency notes, with enhanced security features and other distinctive elements. The new currency notes replace the Birr 10, 50 and 100 notes while an additional Birr 200 note has also been unveiled. The Birr 5 note remains unchanged and will be turned into coin format soon. The currency change is aimed at gathering currency circulating informally and outside of financial institutions; curb corruption and contraband and support financial institutions confront currency shortage.
Most of the print work is currently in country within NBE vault. Distribution mechanism and planning having been developed and will go in effect through concerned bodies. Security plays a key component in the currency change process and relevant authorities together with members of the community will enforce secure implementation. A Federal command post that includes National Defense, NISS and Federal Police will be set up to oversee this process with the expectation that Regional Command Posts will also be set up.
While Ethiopia has never had a symbol to represent its currency, a new symbol has been designed and will be soon unveiled to symbolize the Birr.
(the report is Office of the Prime Minister-Ethiopia on Sept. 14,2020)